የልዑካን ቡድን አባላቱ የካ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ደጃዝማች ወንድይራድ ቅድመ አንደኛ ደረጃ እና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሚገኘው አብዲ ጃርሶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ባካሄዱት ልምድ ልውውጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴን ጨምሮ የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ዳይሬክተር ወይዘሮ በላይነሽ የሻው እና የቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
ልምድ ልውውጡ በዋናነት ከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ሰቶ ተግባራዊ እያደረገ የሚገኘው የቀዳማዊ ልጅነት ፕሮግራም አካል ሆኖ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ የሆነውን በጫወታ የማስተማር ስነ ዘዴ አተገባበርና ተቋማቱን ትራንስፎርም ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ለማየት ታስቦ መካሄዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴን ገልጸው የልዑካን ቡድን አባላቱ በተጨማሪም የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት ሂደትን ተመልክተው መደነቃቸውንም አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሞዴል ለማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት ሀገራቸው ትልቅ ልምድ የምትቀስምበት ተግባር መሆኑን የልዑካን ቡድኑ አባላት በትምህርት ቤቶቹ ተገኝተው ምልከታ ባካሄዱበት ወቅት አመላክተዋል።
.