በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሚገኙ መምህራን ፣ የአስተዳደር አካላት እና የትምህርቱ ማህበረሰቡ አካላት በክፍለ ከተማ ውሰጥ በአጭር ጊዜ ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ የትምሀርት ቤት ማስፋፊያ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።በመድናዋ እየተሰሩ የሚገኙ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች ምቹ፣ ውብና ለኑሮ ተስማሚ እንዲሁም ለትውልድ ግንባታ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸውና የተሻለ ነገን እና የተሻለች ሀገርን ለመፍጠር ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸውን የጉብኝቱ ተሳታፊ መምህራን ገልፀዋል።መምህራኑ ፕሮጀክቶቹ በአጭር ጊዜ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ከመሆናቸው ባሻገር ያላቸው ሀገራዊ ፋይዳም ቀላል እንዳልሆነና የተሻለች ትውልድን ለመገንባትና የተሻለች ሀገር ለመፍጠር ከፍተኛ አስታዋጽኦ እንዳላቸውም አክለው ገልጸዋል።
.