ፈተናው በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 194 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ዘላለሞ ሙላቱ ገልፀዋል።
ሀላፊው በከተማ አስተዳደሩ የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ፈተናውን መውሰድ ካልቻሉ ጥቂት ተማሪዎች በስተቀር አብዛኞቹ ተማሪዎች መፈተናቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም ፈተናው በጭር ጊዜ ውስጥ ታርም ይፋ ይደረጋል ብለዋል።
አያይዘውም በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች የተመደቡ የጸጥታ አካላ ፣ ፈታኞች ፣ የጣቢያ ኃላፊዎች ፣ ሱፐርቫይዘሮችና የፈተና አስፈጻሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ በትጋት በመወጣታቸው ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
.