የጉለሌ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በሀምሌ 19/67 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የልምድ ልውውጥ መርሀግብር አካሄደ።
(ግንቦት 22/2017 ዓ.ም) በልምድ ልውውጡ በክፍለ ከተማው ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ዋና ርዕሳነ መምህራን፣የመማር ማስተማር ምክትል ርዕሳነ መምህራን፣የቅድመ አንደኛ አስተባባሪዎች፣የወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና የትምህርት ቤት መሻሻል ቡድን መሪዎች ፣ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም የመምህራን ማህበር እና የተማሪ ወላጅ ማህበር አመራሮች የተገኙ ሲሆን የትምህርት ቤቱ ዋና ርዕሰ መምህርት ወይዘሪት ሀለወያ ሁሴን በትምህርት ቤቱ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ለታዳሚው አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።
.